Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በደቡብ አፍሪካ በተከሰተው ግጭት 72 ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 7 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ግጭት 72 ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸው ተገልጿል፡፡

የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ በተጠረጠሩበት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል የሀገሪቱ ፍርድ ቤት እንዲታሰሩ ውሳኔ ማሳለፉን በመቃወም በተነሳው ግጭት እና ሁከት የዜጎች ህይወት ሲያልፍ የንብረት መውደም እና ዝርፊያም እየተካሄደ ነው፡፡

ይህን ብጥብጥ ለማስቆም መንግስት እየወሰደ ባለው እርምጃ ብዙዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በሃገሪቱ እየተፈጸመ ያለውን የንጹሃን ዜጎች ግድያ እና የንብረት መውደም እንዲሁም ሁከት አውግዟል፡፡

የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ መሃማት በመግለጫቸው፥ በሃገሪቱ የህግ የበላይነት እንዲከበር እንዲሁም ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን እና በፍጥነት ወደነበረበት እንዲመለስ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version