Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጃኮብ ዙማ የፍርድ ሂደታቸውን በበይነ መረብ ተከታተሉ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ አፍሪካ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የፍርድ ሂደታቸውን በበይነ መረብ ተከታትለዋል፡፡

ዙማ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር ውለው ማረሚያ ቤት መግባታቸው ይታወሳል፡፡

የፍርድ ሂደታቸውን ዳኞች እና እሳቸው በተሳተፈቡት በበይነ መረብ የተካሄደ ሲሆን፥ ዙማም የማረሚያ ቤት ገጽታ በሌለው አንድ ክፍል ውስጥ ሆነው ጉዳያቸውን መከታተላቸውን የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል፡፡

ዙማ የፍርድ ሂደትን በማስተጓጎል ጥፋተኛ ሆነው መገኘታቸውን ተከትሎ ከአንድ ሳምንት በላይ በማረሚያ ቤት ቆይተዋል፡፡

የእርሳቸውን እስር ተከትሎ የተፈጠረ ግርግርም ከ200 በላይ ሰዎች ህልፈት ምክንያት ሲሆን የንብረት ዘረፋ እና ውድመት አስከትሏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version