Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሀዲያ ዞን አሸባሪው ህወሓትን የሚቃወምና መከላከያን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀዲያ ዞን የአሸባሪውን የህወሓት ጁንታን የሚቃወምና መከላከያ ስራዊትን የሚደገፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

በሆሳዕና ከተማ ዛሬ የተካሄደው ሰልፍ ከዞኑ ከሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአስተዳደር አካላት፣ መካላከያ ሰራዊትና የፖሊስ አባላት መሳተፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ሰልፈኞቹ የኢትዮጵያን ክብር አሳልፎ የሚሰጥ ትውልድ የለም፣ የጦር መሳሪያ ከትግራይ ህፃናት ትከሻ ላይ ይውረድ፣ ከመከላከያ ሰራዊት ጎን በመሆን እንደ ሀገር የተጀመረውን ለውጥ እናስቀጥላለን የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በማሰማት ለህወሓት ያላቸውን ተቃውሞና ለመከላከያ ያላቸውን ድጋፍ ገልጸዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version