Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በጎንደር ከተማ ለልዩ ሀይሎች እና ሚሊሻ እንዲሁም ለመከላከያ ሠራዊት የድጋፍ  ሰልፍ  እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ በግንባር እየተዋደቁ ላሉ ልዩ ሀይሎች እና ሚሊሻ እንዲሁም ለመከላከያ ሠራዊት የድጋፍ  ሰልፍ  እየተካሄደ ነው።

የአማራ ሕዝብ ልዩ ኀይሉን ለማጠናከርና ደጀን ለመኾን እያደረገ ያለውን ተነሳሽነት ለማበረታታት የአማራ ፖሊስ የማርች ባንድ አባላትም  በጎንደር ከተማ ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ትርዒት እያሳዩ ነው።

የክልሉን እና የኢትዮጵያን  ሰላም ለመጠበቅ የአማራ ልዩ ኀይል ፖሊስን እንዲቀላቀሉ እና በአማራ ሕዝብ ላይ የተቃጣውን የህልውና አደጋ መመከት እንደሚገባም ጥሪ መቅረቡን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ማስታወቁን አሚኮ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version