Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የግሪክና የሞሮኮ አምባሳደሮች ከኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር አና ፋሩ እና በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር

ኑዝሃ ዓለዊ መሃመዲ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም አምባሳደሮቹ ስለ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች እና እድሎች ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን÷ በቀጣይ ሁለቱ ሀገራት ኢንቨስተሮቻቸውን ወደ ሀገራችን በመላክ የኢንቨስትመንት ፍሰቱን መጨመር ስለሚቻልባቸው መንገዶች መክረዋል፡፡

በተጨማሪም÷ ኢንቨስትመንቱን በጋራ የማስተዋወቅ ስራ ላይ ተወያይተዋል፡፡

ኮምሽነር ለሊሴ ነሜ የኮምሽኑን አዲስ የህንፃ ገፅታ ለአምባሳደሮቹ እንዳስጎበኟቸውም ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version