Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቤሩት ያለሰነድ ይኖሩ የነበሩ 35 ዜጎች ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤሩት ያለሰነድ ይኖሩ የነበሩ 35 ዜጎች ወደ ሃገራቸው ተመለሱ።

ዜጎቹ የኢፌዴሪ ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት ከሊባኖስ የኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት ጋር በመነጋገር ነው ወደ ሃገራቸው የተመለሱት።

በዛሬው እለት ወደ ሃገራቸው የተመለሱት ባለፈው አመት ታህሳስ ወር ላይ ወደ ሃገራቸው ለመመለስ የተመዘገቡና የህክምና ማስረጃ ያቀረቡት መሆናቸውን በቤሩት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version