Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በአንጋፋዉ ድምጻዊ ዓለማየሁ እሸቴ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በአንጋፋዉ ድምጻዊ ዓለማየሁ እሸቴ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ።

ምክትል ከንቲባዋ ‘‘ኢትዮጵያ ታላቅ የጥበብ ሰዉ ነዉ ያጣችው’’ ያሉ ሲሆን÷በአንጋፋዉ ድምጻዊ ዓለማየሁ እሸቴ ህልፈተ ህይወት እጅጉን አዝኛለሁ’’ ሲሉ መልዕክታውን አስተላልፈዋል።

’’ ዓለማየሁ እሸቴ ለሚወዳት ኢትዮጵያ በጥበብ ስራዎቹ ብዙ ያደረገ ሃገር ወዳድ ባለሙያ ነበር’’ ሲሉም ነው የገለጹት።

ምክትል ከንቲባዋ አክለውም ‘’በራሴና በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ስም ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ ልባዊ መፅናናትን እመኛለሁ’’ ብለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version