Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ደመቀ መኮንን በአንጋፋው ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በአንጋፋው ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸውም÷ ለረጅም ዓመታት ትውልድን በሚያንፁ እና ኢትዮጵያን ከፍ በሚያደርጉ የሙዚቃ ስራዎቹ የምናከብረው አንጋፋው ድምፃዊ አለማየሁ እሸቴ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን ሃዘን እገልጻለሁ ብለዋል፡፡

‘’በኢትዮጵያዊ ጨዋነት ያበረከተልን ዘመን ተሻጋሪ የጥበብ ፍሬዎቹ በቀጣይ ትውልድን እያነፁ እንዲሁም የሃገርን ከፍታ እያሳዩ የሚዘልቁ ይሆናል’’ ሲሉም ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው የገለጹት፡፡

በዚህም ለቤተሰቦቹ፣ ለአድናቂዎቹ እና ለኪነ ጥበብ ቤተሰብ በሙሉ መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version