Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የ25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት መወጣት የሚችል ነው – የተመድ ቡድን

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአብዬ የሚገኘው የ25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት መወጣት በሚያስችለው ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተመድ የሰላም አስከባሪ ጦር በአብዬ ኢኒስፔክሽን ቡድን ማረጋገጡ ተገለፀ፡፡

የሻለቃው ዋና አዛዥ ኮሎኔል ሌንጮ ኤደኦ እንደተናገሩት ÷ ቡድኑ ይህንን ማረጋገጡ አመራርና አባላቱ ዛሬም እንደከዚህ በፊቱ የአገራቸውን ክብርና ዝና በማስጠበቅ እውነተኛ የሰላም አምባሳደር መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት የፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version