Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሚኖሩ ስደተኞች የተጠናከረ ድጋፍ ያስፈልጋል- አቶ ደመቀ መኮንን

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተመድ ጠላቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን አቶ ደመቀ በኒውዮርክ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር ፍሊፖ ግራንዴ ጋር ተገናኝተው ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም በስደተኞች አያያዝ፣ በድጋፍ አሰጣጥ እና በስደተኞች ካምፕ አስተዳደር ዙሪያ ጠቃሚ ሃሳቦች ተለዋውጠዋል።

“በኢትዮጵያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመድረስ በቅርበት መስራት ይገባል” ሲሉም አቶ ደመቀ አብራርተውላቸዋል፡፡

በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ለሚኖሩ ስደተኞች ድጋፉን ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመው÷ በቀጣይ የሚያጋጠሙ ችግሮችን ለመሻገር በጋራ መረባረብ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ማስገንዘባቸውን ከጽህፈት ቤታቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version