Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሩሲያ በክህደት የጠረጠረችውን የመረጃ ደህንነት ከፍተኛ ኃላፊ አሰረች

አዲስ አበባ፣ መሰከረም 20፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ)ሩሲያ በክህደት የጠረጠረችውንና ከሀገሪቱ የደህንነት ተቋማት አንዱ የሆነውን የመረጃ ግሩፕ-ኣይ ቢ ኃላፊ አሰረች፡፡
የሩሲያ ፍርድ ቤት በወንጀሉ የተጠረጠረውን ከፍተኛ የመረጃ ደህንነትኃላፊ ኢልያ ሳችኮቭን ለሁለት ወራት በእሰር እንዲቆይ ያዘዘ ቢሆንም÷ በክሶቹ ዝርዝር ላይ እስካሁን ያለው ነገር የለም፡፡
ይሁን እንጅ የ35 ዓመቱ ኢልያ ሳችኮቭ የሩስያ ሚስጥራዊ ሰነዶች ለውጭ አሳልፎ ሰጥቷል በሚል ሳይከሰስ እንዳልቀረ ከምንጮቼ ሰምቻለሁ ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ሳችኮቭ የሚመራው የግሩፕ-አይ ቢ ተቋም የመረጃ ጥቃትን በመከላከል የሚሰራ ሲሆን÷ እንደ ኢንተርፖል የመሳሰሉ ትላልቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ደምበኞቹ ናቸው፡፡
ተጠርጣሪው ወንጀለኛ ሆኖ ከተገኘ በሩስያ ህግ መሰረት እስከ 20 ዓመት የእስር ቅጣት የሚበየንበት ይሆናል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version