Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የግሸን ደብረ ከርቤ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣መስከረም21፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የግሸን ደብረ ከርቤ ዓመታዊ ክብረ በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶች እየተከበረ ነው፡፡
አሚኮ እንደዘገበው የሃይማኖቱ ተከታዮች በዓሉ አስተማማኝ በሆነ የሰላም ሁኔታ እየተከበረ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተገኙ ምዕመናን፥ በዓሉን ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ እያከበረ መሆኑን  ነው የተናገሩት፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የታደሙ የሃይማኖት አባቶች እና የሃይማኖቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version