Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የማዕረግ ተሿሚዎች ለተጨማሪ ግዳጅና ሀላፊነት ራሳችሁን ማዘጋጀት ይገባል – ብ/ጄ ዶ/ር ሀይሉ እንዳሻው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የጦር ሀይሎች ኮምፕሬሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሻለ የስራ አፈፃፀምና የመቆያ ጊዜያቸውን ለሸፈኑ አመራሮችና አባላት የማዕረግ ዕድገት ሰጠ፡፡

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የሆስፒታሉ አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል ዶክተር ኃይሉ እንዳሻው ተሿሚዎች ለበለጠ ኃላፊነትና ለተጨማሪ ግዳጆች ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል።

ማዕረግ ባደገ ቁጥር ለህዝባችን ያለን ታማኝነት፣ ተቆርቋሪነትና ታታሪነት በመጨመር የበለጠ ሀገራችንን ለማገልገል ራሳችንን ማዘጋጀት ይገባል ብለዋል፡፡

በዚሁ መሠረትም ተሿሚዎች በሁሉም መስክ ራሳችሁን ማዘጋጀት ይኖርባችኋል ነው ያሉት፡፡

ተሿሚዎችም የማዕረግ ዕድገቱ እንዳስደሰታቸውና ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነትም በበለጠ ሁኔታ ለመወጣት ዝግጁ ነን ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version