Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

መውሊድ በደሴ ከተማ የሙስሊም እና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በተገኙበት በጋራ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 496ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዕ.ወ) የመውሊድ በዓል በደሴ ከተማ የክርስትና እና የሙስሊም ሃይማኖት ተከታዮች በተገኙበት በጋራ ተከብሯል፡፡

የደሴ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ሊቀመንበር ሼህ ሰይድ ኡመር እንኳን ለ1 ሺህ 496ኛው የነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

አሚኮ እንደዘገበው÷ የመውሊድ በዓልን ለመከላከያ ሠራዊቱ ድጋፍ በማድረግ፣ ለተፈናቀሉ ወገኖች ማድ በማጋራት እና ሌሎች በጎ ተግባራትን በመከወን መከበሩን ገልጸዋል።

ለዚህም ሕዝበ ክርስቲያኑ እና ሙስሊሙ ድጋፍ ማድረጋቸውን አስረድተዋል። ማኅበረሰቡም የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት በዓሉን እንዲያሳልፍ ጠይቀዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version