Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኦብነግ ለአቶ ሙስጠፌ የእንኳን ደስአለዎት መልዕክት አስተላለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ለአቶ ሙስጠፌ መሐመድ የሶማሌ ክልል ርዕሠ መስተዳድር ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስአለዎት መልዕክት አስተላለፈ፡፡
ፓርቲው ባስተላለፈው መልዕክት ከክልመንግሥት ጋር አብሮ ለመሥራት ያለውን ቁርጠኝነት አመላክቷል፡፡
ለክልሉ ዘላቂ ሠላምና ልማት የአቶ ሙስጠፌ ወደፊት መምጣት ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብሏል፡፡
በአጠቃላይ ኦብነግ ከሶማሌ ክልል አዲሱ መንግስት ጋር አብሮ መሥራቱን ይቀጥላል ያለው መግለጫው÷ በጋራ መተማመን ላይ የተመሰረተ ገንቢ ሥራዎችን እንደምንሠራ እምነታችን ነው ብሏል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version