Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኃላፊነት የጎደላቸው የማህበራዊ ትስስር ገፆችንና ‘ማህበራዊ አንቂ ነን’ የሚሉ ግለሰቦችን እንደማይታገስ መንግስት አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)ኃላፊነት የጎደላቸው የማህበራዊ ትስስር ገፆችን እና ‘ማህበራዊ አንቂ ነን’ የሚሉ ግለሰቦችን እንደማይታገስ መንግስት አስታውቋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጠው መግለጫ መንግስት ያቀረበውን ሀገርን የመታደግ ጥሪ ተከትሎ ህዝቡ እና የመንግስት ሰራተኛው በነቂስ ዘመቻውን እየተቀላቀለ መሆኑን ገልጿል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ÷ የህብረተሰብን ሰላም እና ደህንነት የሚያውኩ ሆነው እስከተገኙ ድረስ መንግስት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚደረግ ማንኛውንም እንቅስቃሴ አይታገስም ማለታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version