Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሶማሌ ክልል ድርቅ ለተከሰተባቸው አካባቢዎች የሚውል 200 ሚሊየን ብር አጸደቀ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ካቢኔ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እና አስፈላጊውን እርዳታ ለማድረስ የሚውል 200 ሚሊየን ብር አፀደቀ፡፡

ካቢኔው ገንዘቡን ያጸደቀው ዛሬ በጎዴ ባካሄደው 7ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ ነው፡፡

ካቢኔው በተለያዩ ወቅታዊ ፣ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ የመከረ ሲሆን፥ በተለይ በክልሉ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች አስቸኳይ ምላሽ መስጠት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ በስፋት መምከሩን ከክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version