Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከ2 ሺህ በላይ የመዲናዋ ወጣቶች በአገራዊ ወቅታዊ ጉዳይ እየመከሩ ነው

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 4 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ከከተማዋ ሰላምና ጸጥታ፣ ፖሊስ ኮሚሽን እና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች ጋር በአገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየመከረ ነው።
የመዲናዋ የሰላም ዘብ የሆኑ ወጣቶች እያካሄዱት የሚገኘው ምክክርም “በመረረ ትግላችን ጣፋጭ ድል እናጣጥማለን” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።
በምክክር መድረኩም የፌደራል እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የመዲና ወጣቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
-አካባቢህን ጠብቅ
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version