Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጌዴኦ ዞን ዲላ መስጂዶች ማኅበር ለተፈናቃይ ወገኖች የአይነት ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ መስጂዶች ማኅበር የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተጎጂዎች የአይነት ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉ ምግብ ነክ ፣ አልባሳትና የቤት መገልገያ ቁሳቁሶችን ያካተተ ሲሆን በ2 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ወጪ የተገዛ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ መስጂዶች ማኅበር ÷ ያቀረበውን እርዳታ ከአባላቱና ከማኅበረሰቡ ያሰባሰበው መሆኑን የማህበሩ አመራሮች በርክክቡ ወቅት ገልፀዋል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version