Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በሰላም ግንባታ ላይ ለሚያከናውነው ተግባር ከ13 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ስተርሊንግ ፋውንዴሽን የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰላም ግንባታና ግጭት አፈታት ዙሪያ ለሚያከናውነው ተግባር የሚውል ከ13 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እ.አ.አ በ2022/23 በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ሊሰራው ያሰበውን የሰላም ግንባታ፣ የግጭት አፈታትና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችን የሚያጠናክር የበጀት ድጋፍ እንደተደረገለት የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ጉባዔው የበጀት ድጋፉን ያገኘው መቀመጫውን በአሜሪካ ዩታ ግዛት ካደረገው ስተርሊንግ ፋውንዴሽን ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን ነው የገለጹት።
ጉባዔው ዕቅዱን ለመፈጸም የሀብት ማፈላለጊያ የፕሮጀክት ፕሮፖዛል በማዘጋጀት ለፋውንዴሽኑ የላከ ሲሆን÷ ፋውንዴሽኑም ፕሮጀክቱን በመቀበል፣ የበጀት ድጋፍ ለማድረግ ፈቅዷል ነው ያሉት።
በዚህም መሠረት ጉባዔውና ፋውንዴሽኑ የድጋፍ ስምምነት ፊርማ ዛሬ በአሜሪካ ዮታ ግዛት አከናውነናል ብለዋል።
ፋውንዴሽኑ ከዚህ በፊትም ለጉባዔው ልዩ ልዩ ድጋፎችን ማድረጉን አስታውሰው÷ በቅርቡም ለጉባዔው ተሽከርካሪ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version