Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የተመድ ዋና ፀሃፊ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን ለማቀላጠፍ ግጭት ለማቆም መወሰኑን አደነቁ

Secretary-General António Guterres briefs reporters on the war in Ukraine. “Ukraine is on fire. The country is being decimated before the eyes of the world. The impact on civilians is reaching terrifying proportions… […] It’s time to stop the horror unleashed on the people of Ukraine and get on the path of diplomacy and peace.“ said the Secretary-General.

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን ለማቀላጠፍ ግጭት ለማቆም መወሰኑን አደነቁ።

ጉተሬዝ በቃል አቀባያቸው በኩል ባወጡት መግለጫ መንግስት የሰብዓዊ ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የሚላከውን አቅርቦት ማሳለጥ እንዲቻል ግጭት ማቆሙን በአወንታ እንደሚቀበሉት አስታውቀዋል።

ግጭት በአፋር፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ኦሮሚያ ክልሎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለችግር መዳረጉን ያነሱት ዋና ፀሃፊው፥ የመንግስትን መልካም ውሳኔ ሁሉም ወገን ወደ መሬት እንዲያወርደው ነው ያሳሰቡት።

በብርቱ የሚያስፈልገውን የሰብዓዊ እርዳታን በእነዚህ በግጭት የተጎዱ አካባቢዎች ለማድረስ ሁሉም ወገን እንዲረባረብም ነው ጥሪ ያቀረቡት።

የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን ለማቀላጠፍ ግጭት ለማቆም መወሰኑን ከትናንት በስቲያ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

Exit mobile version