Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የእሁድ ገበያ የዋጋ ንረት በማረጋጋት እና የኑሮ ጫና በመቀነስ ረገድ ጉልህ ሚና እየተወጣ ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የእሁድ ገበያ ወደ 50 ቦታዎች ላይ መስፋፋቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቀ።
ከንቲባዋ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ “አሁን ያለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት እና በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች ያለባቸውን የኑሮ ጫና በመቀነስ ረገድ ጉልህ ሚና እየተወጣ ይገኛል” ብለዋል፡፡
አቅርቦቱን በመጨመርና በማስፋት ይበልጥ ወደ ህዝቡ እንዲቀርብ በትኩረት ሰጥተን እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
በየክፍለከተማው የእሁድ ገበያ እንዲስፋፋና እንዲለመድ ላስተባበሩ፣ ለመሩ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና አቅራቢዎች ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version