Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

5 ሺህ ኪሎ ግራም በሚጠጋ ቅቤ ውስጥ ባዕድ ነገር ቀላቅለው ሊሸጡ በነበሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓላትን አስታከው 5 ሺህ ኪሎ ግራም በሚጠጋ ቅቤ ላይ ባዕድ ነገር ቀላቅለው ሊሸጡ በነበሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ፡፡
ሰሞኑን በሚዛን አማን ከተማ፣ በካፋ እና በቤንቺ ሸኮ ዞኖች በተካሄደ የዘመቻ ሥራ÷ 2 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ግምት ያለው 4 ሺህ 849 ኪሎ ግራም ከባዕድ ነገር ጋር የተቀላቀለ ቅቤ ተይዟል፡፡
በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት በተሳተፉ 30 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ መወሰዱን ከኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከባዕድ ነገር ጋር ተቀላቅሎ የተያዘው ቅቤ ለህብረተሰቡ ቢደርስ ከፍተኛ የጤና ችግር ያስከትል እንደነበርም ነው የተመላከተው፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version