Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አርቲስት ዘነቡ ገሠሠ ከዚህ አለም በሞት ተለየች

 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አርቲስት ዘነቡ ገሠሠ ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች፡፡

አርቲስቷ ባደረባት የጡት ካንሰር ህመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ነው በዛሬው ዕለት ሕይወቷ ማለፉ የተሰማው፡፡

አርቲስት ዘነቡ ገሠሠ በርካታ የጥበብ ሥራዎች ላይ በመሳተፍ እና ድንቅ ብቃቷን በማሳየት አድናቆትን አትርፋለች፡፡

አርቲስት ዘነቡ የሁለት ሴቶች እና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ነበረች ፡፡

የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ነገ ሚያዝያ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 9:00 ሰዓት በቡልቡላ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ለማወቅ ተችሏል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትም በአርቲስቷ ሞት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ÷ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለአድናቂዎቿ መፅናናትን ይመኛል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version