Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀን በአዲስ አበባ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት13፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2019 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቅጥር ግቢ ውስጥ ተከብሯል።

በበዓሉ  የተመድ ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሃመድ፣ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት  ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።

በአከባበር ስነ ስርዓቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል መርሃ ግብር ተከናውኗል።

Exit mobile version