Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አትሌት ሰምበሬ ተፈሪ በአሜሪካ አትላንታ በተደረገ የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሰምበሬ ተፈሪ በአሜሪካ አትላንታ በተደረገ የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር ቀዳሚ በመሆን አሸንፋለች፡፡

አትሌቷ ርቀቱን 30 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው  ቀዳሚ ሆና የጨረሰችው፡፡

በውድድሩ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጀማል ይመር በወንዶች  ምድብ በተመሳሳይ ርቀት 3ኛ በመሆን ማጠናቀቁን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version