አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1ሺህ 65 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢው ድጋፍ እና እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት መሄዳቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
እስካሁን ድረስ በተከናወነ ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ÷ 65 ሺህ 14 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገልጿል፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!