Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ደመቀ መኮንን ከእንግሊዝ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 11 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከእንግሊዝ የአፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባህር ልዩ መልዕክተኛ ሳራ ሞንትጎመሪ ጋር ተወያዩ።

በውይይቱም እንግሊዝ ከኢትዮጵያ ጋር ስላላት የረጅም ጊዜ ወዳጅነት አስታውሰው፥ በእንግሊዝ መንግስት በኩል እየቀረበ ላለው ዘርፈ ብዙ ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ የሰሜኑ ክፍል የተፈጠረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መንግስት ቁርጠኛ መሆኑን በመጥቀስም፥ ችግሩን ለመፍታት በመንግስት በኩል እየተወሰዱ ስላሉ ዝርዝር ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

የእንግሊዝ የአፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባህር ልዩ መልዕክተኛ ሳራ ሞንትጎመሪ በበኩላቸው የመጀመሪያቸው በሆነው ጉዞ ብዙ ነገሮች ላይ ግንዛቤ እንዳገኙ ጠቅሰዋል።

በሃላፊነታቸው በሀገራቱ መካከል ያለው የረጅም ጊዜ ወዳጅነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንደሚወጡ መናገራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

የሰላም ሂደቱን ለመደገፍም ዝግጁ መሆናቸው አስረድተዋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version