Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አየር መንገዱ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል ከፈተ 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል መክፈቱን አስታወቀ፡፡

ሆቴሉ ከመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል -ሁለት ጋር የተገናኘና ለመሳፈሪያ በሮችም  ቅርብ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሆቴሉ ግንባታ በፈረንጆቹ 2020 ታህሳስ ወር ላይ የተጀመረ ሲሆን ÷ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ተመላክቷል፡፡

ሆቴሉ በውስጡ 41 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች እንዳሉትም ነው የተገለጸው፡፡

ሆቴሉ በስካይላይት ሆቴል ሥር የሚተዳደር መሆኑንም ከአየር መንገዱ  ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

 

Exit mobile version