Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም የቱሪዝም ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በአሶሳ ከተማ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የቱሪዝም ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ “አዲስ እሳቤ ለቱሪዝም ” በሚል መሪ ቃል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ በሚገኘው በዚህ በዓል ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊን ጨምሮ የተለያዩ የፌደራልና የክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

ዘርፉ በኮቪድ 19 እና በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት እንዲያገግም የሚያስችል ሀገር አቀፍ የቱሪዝም ንቅናቄ እንደሚጀመርም ይጠበቃል።

የዓለም የቱሪዝም ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መከበሩ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ለሚሰራው ስራ እንዲሁም የክልሉን የመስህብ ስፍራዎች ከማስቀዋወቅ አንፃር አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

በላምሮት የኔዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version