Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ በተመረጡ መስመሮች ብቻ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል

የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ በተመረጡ መስመሮች ብቻ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል

 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

 

የቢሮው መረጃ እንዳመላከተው÷ ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ የአንበሳ፣ የሸገር ድጋፍ ሰጪ እና የፐብሊክ ሰርቪስ አውቶቡስ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ይሰጣሉ፡፡

 

በዚህም መሰረት÷ ከአባኪሮስ ዐደባባይ፣ አያት ዐደባባይ፣ ቱሉ ዲምቱ ዐደባባይ፣ ጎሮ ዐደባባይ፣ አዲሱ ገበያ፣ ቁስቋም፣ ሳንሱሲ፣ አየር ጤና ዐደባባይ እና ጀሞ ዐዳባባይ ተሳፋሪዎች የትራንስፖርት አገልገሎቱን ማግኘት ይችላሉ፡፡

 

Exit mobile version