የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ በተመረጡ መስመሮች ብቻ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል
የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ በተመረጡ መስመሮች ብቻ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ በተመረጡ መስመሮች የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው መረጃ እንዳመላከተው÷ ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ የአንበሳ፣ የሸገር ድጋፍ ሰጪ እና የፐብሊክ ሰርቪስ አውቶቡስ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ይሰጣሉ፡፡
በዚህም መሰረት÷ ከአባኪሮስ ዐደባባይ፣ አያት ዐደባባይ፣ ቱሉ ዲምቱ ዐደባባይ፣ ጎሮ ዐደባባይ፣ አዲሱ ገበያ፣ ቁስቋም፣ ሳንሱሲ፣ አየር ጤና ዐደባባይ እና ጀሞ ዐዳባባይ ተሳፋሪዎች የትራንስፖርት አገልገሎቱን ማግኘት ይችላሉ፡፡