Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ ለመከላከያ ሠራዊት ከ112 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ ለመከላከያ ሠራዊት ከ112 ሚሊየን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በዓይነት ድጋፍ አደረጉ፡፡

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ድጋፉን ለመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ አስረክበዋል።

ድጋፉ 110 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲሆን ከ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ያህሉ ደግሞ የዓይነት ነው፡፡

ዶክተር ሊያ እንደገለጹት÷ ለኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት ለሚዋደቀው ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት ሁለንተናዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን፡፡

ባለፉት ሁለት ወራት ከ118 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የመድኃኒት ስርጭት መደረጉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version