Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በመንገሺ ወረዳ እየለማ የሚገኝ የስንዴ ማሳን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 6 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በማጃንግ ዞን መንገሺ ወረዳ በሙከራ ደረጃ እየለማ የሚገኝ የስንዴ ማሳን ጎብኝተዋል፡፡
 
በመርሐ ግብሩ የተሳተፉት ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ÷ የጋምቤላ ክልል በስንዴ ምርት ከሁሉም ክልሎች ወደ ኋላ መቅረቱን አንስተዋል።
 
በአሁኑ ሰዓት በተለያየ የክልሉ አካባቢዎች ስንዴን በስፋት ለማምረት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው÷ በሙከራ ደረጃ ያለው ተግባር ውጤት ካስገኘ በስፋት እንደሚከናወን አመልክተዋል።
 
የማጃንግ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ማይክል በበኩላቸው÷ የስንዴ ምርት በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት እንደሚገኝ ጠቁመው÷ በዞኑም በ20 ሄክታር መሬት ላይ ሙከራ መደረጉን አስታውቀዋል።
 
የሙከራ ሂደቱ ውጤታማ መሆን ከቻለ ወደ ሌሎች ቀበሌዎች የማስፋቱ ስራ እንደሚከናወን የገለጹት አቶ አብርሃም÷ ሙከራው ተስፋ ሰጪ እንደሆነ አብራርተዋል።
 
የአካባቢው መሬት ለበርካታ አዝዕርት ምቹ መሆኑ እና የሙከራ ስንዴው በ90 ቀናት ሊደርስ የሚችል ዝርያ እንደሆነ መገለጹንም ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
Exit mobile version