አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢሲ)በኢትዮጵያ መንግስት እና በሕህወት መካከል የተደረገውን የሰላም ስምምነት እናደንቃለን ሲሉ የቤልጅየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃጃ ላቢብ ተናገሩ፡፡
ሚኒስትሯ በትዊትር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት የተደረሰውን የሰላም ስምምነት በደስታ እንቀበለዋለን ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት እና ደቡብ አፍሪካ የሰላም ንግግሩ እንዲሳካ ላደረጉት ጥረትም ሚኒስትሯ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡