Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከታች ከቀረበው በመንግስት እና በህወሓት በኩል ከተፈረመው የሠላም ስምምነት ውጪ የተሰራጩ መረጃዎች ያልተሟሉና ሊያሳስቱ የሚችሉ ናቸው – አምባሳደር ሬድዋን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በመንግስት እና በህወሓት መካከል የተደረሰውን ትክክለኛ ስምምነት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አጋርተዋል።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ÷ ስምምነቱ የተፈረመው ከበርካታ እልህ አስጨራሽ የቡድን ክርክሮች እና ንግግሮች በኋላ መሆኑን መገንዘብ ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም ከሁለቱ ተወያይ ወገኖች የቀረቡ በርካታ ረቂቆች የነበሩ ቢሆንም ስምምነት ላይ የተደረሰበት እና ተቀባይነት አግኝቶ የተፈራረምንበት ሠነድ ግን ከዚህ በታች የተቀመጠው ነው ሲሉም አስታውቀዋል።

አምባሳደር ሬድዋን እየተሰራጩ ያሉት መረጃዎች ቀደም ብለው የተዘጋጁ መረጃዎች ሊሆኑ እንደሚችሉም ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version