አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ6ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ድሬዳዋ ላይ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
10 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ እና መቻል ባደረጉት ጨዋታ ወላይታ ድቻ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግብ ቃልኪዳን ዘላለም በ31ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ወልቂጤ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የወልቂጤ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች ጌታነህ ከበደ በ21ኛው እና 52 ኛው ደቂቃ ላይ ሲያሥቆጥር÷ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ደግሞ ታፈሰ ሰርካ በተጨማሪ ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!