Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በፕሪሚየር ሊጉ ወላይታ ድቻ እና ወልቂጤ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ6ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ድሬዳዋ ላይ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡

10 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ እና መቻል ባደረጉት ጨዋታ ወላይታ ድቻ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግብ ቃልኪዳን ዘላለም በ31ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡

ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ወልቂጤ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የወልቂጤ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች ጌታነህ ከበደ በ21ኛው እና 52 ኛው ደቂቃ ላይ ሲያሥቆጥር÷ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ደግሞ ታፈሰ ሰርካ በተጨማሪ ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version