Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

17ኛው የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባዔ በኢንዶኔዢያ ዛሬ ይጠናቀቃል

Indonesia President Joko Widodo, center, speaks during the G20 leaders summit in Nusa Dua, Bali, Indonesia, Tuesday, Nov. 15, 2022. Dita Alangkara/Pool via REUTERS

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባዔ በኢንዶኔዢያ ባሊ እየተካሄ ነው።

በዛሬው ዕለት በጉባዔው የሚነሱ የውይይት ነጥቦች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያተኩራሉ ተብሏል፡፡

“በአንድነት እናገግም፣ እንጠንክር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኘው የሀገራቱ ጉባዔ ዛሬ ይጠናቀቃል መባሉን የዘገበው ሲ ጂ ቲ ኤን ነው፡፡

ከጉባዔው በፊት የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ እና የአሜሪካው አቻቸው ጆ ባይደን ፊት ለፊት ተገናኝተው በወቅታዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version