17ኛው የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባዔ በኢንዶኔዢያ ዛሬ ይጠናቀቃል
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባዔ በኢንዶኔዢያ ባሊ እየተካሄ ነው።
በዛሬው ዕለት በጉባዔው የሚነሱ የውይይት ነጥቦች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያተኩራሉ ተብሏል፡፡
“በአንድነት እናገግም፣ እንጠንክር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኘው የሀገራቱ ጉባዔ ዛሬ ይጠናቀቃል መባሉን የዘገበው ሲ ጂ ቲ ኤን ነው፡፡
ከጉባዔው በፊት የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ እና የአሜሪካው አቻቸው ጆ ባይደን ፊት ለፊት ተገናኝተው በወቅታዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡