Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ወሳኝ የምድብ ድሏን አስመዘገበች

DOHA, QATAR - NOVEMBER 27: Abdelhamid Sabiri of Morocco celebrates after scoring their team's first goal during the FIFA World Cup Qatar 2022 Group F match between Belgium and Morocco at Al Thumama Stadium on November 27, 2022 in Doha, Qatar. (Photo by Buda Mendes/Getty Images)

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ቤልጂየምን 2 ለ 0 በማሸነፍ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች፡፡

በጨዋታው ብርቱ ተፎካካሪ ሆና የቀረበችው የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ ከእረፍት መልስ አብዱልሃሚድ ሳብሪል እና ዛካሪያ አቡክላል ባስቆጠሯቸው ጎሎች ቤልጂየምን በማሸነፍ ወሳኝ ድል አስመዝግባለች፡፡

ሞሮኮ ከሴኔጋል በመቀጠል በዓለም ዋንጫው ማሸነፍ የቻለች አፍሪካዊት ሀገር ስትሆን ከምድቡ አራት ነጥብ በመያዝ ከወዲሁ የማለፍ እድሏን አስፍታለች፡፡

ቤልጂየም በምድቡ ሶስት ነጥብ ያላት ሲሆን÷ ከምድቡ ለማለፍ ቀጣይ ጨዋታዎችን የምትጠበቅ ይሆናል፡፡

በዚሁ የምድብ ስድስት ጨዋታ ምሽት አንድ ሰዓት ክሮሺያ ከካናዳ ጨዋታቸውን ሲያደርጉ ምሽት 4 ሰዓት ደግሞ በምድብ አምስት ስፔን ከጀርመን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

 

 

 

 

Exit mobile version