Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

 ብራዚል ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏን አረጋገጠች

Soccer Football - FIFA World Cup Qatar 2022 - Group G - Brazil v Switzerland - Stadium 974, Doha, Qatar - November 28, 2022 Brazil's Casemiro celebrates scoring their first goal with Vinicius Junior REUTERS/Marko Djurica

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ ብራዚል እና ስዊዘርላንድ ምሽት ላይ የምድብ ሁለት ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡

በዚህም ብራዚል ስዊዘርላንድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በምድቡ ያላትን ነጥብ ወደ ስድስት ከፍ አድርጋለች፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ከፈረንሳይ በመቀጠል ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች ሁለተኛ ሀገር መሆን ችላለች፡፡

የብራዚልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ካሰሚሮ 83ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡

Exit mobile version