![](https://sp-ao.shortpixel.ai/client/to_webp,q_lossy,ret_img/https://www.fanabc.com/wp-content/uploads/2022/11/WOW-750x430.jpg?v=1669657849)
ብራዚል ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏን አረጋገጠች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ ብራዚል እና ስዊዘርላንድ ምሽት ላይ የምድብ ሁለት ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡
በዚህም ብራዚል ስዊዘርላንድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በምድቡ ያላትን ነጥብ ወደ ስድስት ከፍ አድርጋለች፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ከፈረንሳይ በመቀጠል ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች ሁለተኛ ሀገር መሆን ችላለች፡፡
የብራዚልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ካሰሚሮ 83ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡