Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ብራዚል ደቡብ ኮሪያን 4 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

Soccer Football - FIFA World Cup Qatar 2022 - Round of 16 - Brazil v South Korea - Stadium 974, Doha, Qatar - December 5, 2022 Brazil's Neymar celebrates scoring their second goal with Vinicius Junior, Raphinha and Lucas Paqueta REUTERS/Carl Recine

 

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል እና ደቡብ ኮሪያ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡

በዚህም የአምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮኗ ብራዚል ደቡብ ኮሪያን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡

የብራዚልን የማሸነፊ ግቦች ቪኒሺየስ ጁኒየር፣ ኔይማር ጁኒየር፣ሪቻርሊሰን እና ሉካስ ፓኪዮታ በ7ኛው፣ በ13ኛው፣በ29ኛው እና በ36ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረዋል፡፡

የደቡብ ኮሪያን ብቸኛ ግብ ደግሞ ፓይክ ሰንግ 76ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡

ቀደም ሲል በተደረገ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ክሮሺያ ጃፓንን በመለያ ምት 3 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡

በቀጣይ ለሚካሄደው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታም ብራዚል ክሮሺያን የምትገጥም ይሆናል፡፡

Exit mobile version