በዓለም ዋንጫው ዛሬ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታወች ይካሄዳሉ Melaku Gedif 1 year ago አዲስ አበባ፣ ሕዳር 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር የዓለም ዋንጫ በዛሬው ዕለት ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታወች ይካሄዳሉ፡፡ በዚህ መሰረትም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ብራዚል ከክሮሺያ ለግማሽ ፍጻሜው ለመድረስ ጨዋታቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል፡፡ መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርጀንቲና ከኔዘርላንድስ የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል፡፡