በዓለም ዋንጫው ዛሬ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታወች ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር የዓለም ዋንጫ በዛሬው ዕለት ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታወች ይካሄዳሉ፡፡
በዚህ መሰረትም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ብራዚል ከክሮሺያ ለግማሽ ፍጻሜው ለመድረስ ጨዋታቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል፡፡
መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርጀንቲና ከኔዘርላንድስ የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል፡፡