Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አርጀንቲና የኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች

LUSAIL CITY, QATAR - DECEMBER 18: Players of Argentina celebrates in front of their fans after defeating France in the penalty shootout to win the World Cup Final during the FIFA World Cup Qatar 2022 Final match between Argentina and France at Lusail Stadium on December 18, 2022 in Lusail City, Qatar. (Photo by Tullio Puglia - FIFA/FIFA via Getty Images)

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አርጀንቲና ፈረንሳይን በመለያ ምት በማሸነፍ የኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆናለች፡፡
 
የ22ኛው የኳታር ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሉሳይል አይኮኒክ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡
 
በዚህም ፈረንሳይ እና አርጀንቲና መደበኛ ጨዋታውን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ያጠናቀቁ ሲሆን÷ ተጨማሪ 30 ደቂቃውንም 3 ለ 3 አቻ ተለያይተዋል፡፡
 
የፍጻሜ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠ የመለያ ምትም አርጀንቲና ፈረንሳይን በማሸነፍ ከ36 ዓመታት በኋላ የዓለም ዋንጫን ማንሳት ችላለች፡፡
 
ድራማዊ ትዕይንት ባስተናገደው የፍጻሜ ጨዋታ ኬሊያን ምባፔ ከ92 ዓመታት በኋላ በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ሀትሪክ መስራት ችሏል፡፡
 
ድራማዊ ትዕንት ባስተናገደው የፍጻሜ ጨዋታ ኬሊያን ምባፔ ከ92 ዓመታት በኋላ በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ሀትሪክ መስራት ችሏል፡፡
 
ምባፔ በ22ኛው የኳታሩ የዓለም ዋንጫም ስምንት ግቦችን በማስቆጠር ኮከብ ጎል አግቢ መሆን ችሏል።
Exit mobile version