Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

እስራኤል በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ላይ ማሻሻያ ልታደርግ ነው

FILE - Benjamin Netanyahu, former Israeli Prime Minister and the head of Likud party, speaks to his supporters after first exit poll results for the Israeli Parliamentary election at his party's headquarters in Jerusalem on Nov. 2, 2022. Netanyahu's Likud party released the new government's policy guidelines on Wednesday, Dec. 28, 2022. Netanyahu’s incoming hard-line government has put West Bank settlement expansion at the top of its list of priorities a day before it's set to be sworn into office. (AP Photo/Oren Ziv, File)

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራኤል ለውጭ ሃይሎች ተጽዕኖ ሳትንበረከክ ብሄራዊ ጥቅሟን ታስከብራለች ሲሉ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ተናገሩ፡፡

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተመረጡት ኔታንያሁ በቅርቡ አዲስ መንግስት መስርተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ  በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ÷ እስራኤል ከዚህ ቀደም በነበራት  የውጭ  ጉዳይ ፖሊሲ ላይ ማሻሻያ እንደምታደርግ  አስታውቀዋል፡፡

በቀጣይ የሚወጣው የሀገሪቱ  የውጭ ጉዳይ ፖሊስም  የእስራኤልን ሉዓላዊነት እና ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ መሆኑ ነው ያብራሩት፡፡

ለዓለም አቀፍ ጫናዎች አንበረከክም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ የእስራኤልን ግዛት ለማስከበር እና ተጽእኖ ፈጣሪ ሆኖ ለመዝለቅ በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል፡፡

ከውጭ ሀገራት ጋር የሚኖረው ሁለንተናዊ ግንኙነትም የጋራ ጥቅምን ባስከበረ መልኩ እንደሚሆን አጽንኦት  መስጠታቸውን አር ቲ ዘግቧል፡፡

Exit mobile version