Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ቻይና በኮቪድ-19 ሳቢያ ያሳለፈችውን የውጭ ሀገር የጉዞ ገደብ አነሳች

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ያሳለፈችውን የውጭ ሀገራት የጉዞ ገደብ አነሳች፡፡

ከአሁን በኋላ ወደ ቻይና የሚገቡ የውጭ ሀገር ተጓዦች ቀደም ሲል በተቀመጠው የኮቪድ -19 አስገዳጅ መመሪያ መሠረት በለይቶ ማቆያ ለአምሥት ቀናት እንደማይቀመጡ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

ቢጂንግ ገደቡን ካነሳች ወዲህ የመጀመሪያዎቹን 387 መንገደኞች ከሲንጋፖር እና ከካናዳዋ ቶሮንቶ ከተማ መቀበሏ ተመላክቷል፡፡

መንገደኞቹም ቀደም ሲል በሀገሪቷ በተጣለው የኮቪድ -19 ገደብ መሠረት ሳይንገላቱ ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ነው የተገለጸው፡፡

ቀደም ሲል ቻይና እየተባባሰ በሄደው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት ምክንያት ድንበሮቿን ላለፉት ሦስት ዓመታት ዘግታ መቆየቷ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version