አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ወታደራዊ ልምምዶችን በታይዋን አቅራቢያ ማካሄዷን አስታውቃለች፡፡
ቤጂንግ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ የአሁኑን ጨምሮ ሁለት ወታደራዊ ልምምዶችን በታይዋን አቅራቢያ ማካሄዷ ተገልጿል፡፡
ልምምዶቹ የሀገሪቷን የዓየር ፣ የምድር እና የባሕር ኃይሎች ብቃት ለመፈተሽ የተካሄዱ መሆናቸውን የቻይና ምሥራቃዊ ዕዝ ጦር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ሺ ዪ ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም ጥምር ልምምዶቹ ሌሎች የውጭ ኃይሎችና የታይዋን ተገንጣዮች ለሚቃጡት ግጭት ቀስቃሽ እርምጃ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ለማስተላለፍ ያለመ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የታይዋን ፕሬዚዳንት ጽኅፈት ቤት በበኩሉ÷ ድርጊቱን መሰረተ ቢስ ውንጀላ ሲል ማጣጣሉን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!