Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ቻይና በታይዋን አቅራቢያ ተጨማሪ ወታደራዊ ልምምድ አካሄደች

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ወታደራዊ ልምምዶችን በታይዋን አቅራቢያ ማካሄዷን አስታውቃለች፡፡

ቤጂንግ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ የአሁኑን ጨምሮ ሁለት ወታደራዊ ልምምዶችን በታይዋን አቅራቢያ ማካሄዷ ተገልጿል፡፡

ልምምዶቹ የሀገሪቷን የዓየር ፣ የምድር እና የባሕር ኃይሎች ብቃት ለመፈተሽ የተካሄዱ መሆናቸውን የቻይና ምሥራቃዊ ዕዝ ጦር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ሺ ዪ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ጥምር ልምምዶቹ ሌሎች የውጭ ኃይሎችና የታይዋን ተገንጣዮች ለሚቃጡት ግጭት ቀስቃሽ እርምጃ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ለማስተላለፍ ያለመ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

የታይዋን ፕሬዚዳንት ጽኅፈት ቤት በበኩሉ÷ ድርጊቱን መሰረተ ቢስ ውንጀላ ሲል ማጣጣሉን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version