Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ክልል የ2015 የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል የ2015 የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በዛሬው ዕለት በአዳማ ወረዳ ተካሂዷል፡፡

በመርሐ ግብሩ የብልጽግና ፓርቲ ኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኤልያስ ከድር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት ÷ ዘመቻው በሁሉም የኦሮሚያ ክልል ዞኖችና ወረዳዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በዘንድሮው የልማት መርሐ-ግብር በኦሮሚያ ክልል በተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ልማት ሥራ 3 ሚሊየን 224 ሺህ ሄክታር መሬት እና 6 ሺህ 448 ተፋሰሶችን ለማልማት መታቀዱን ኃላፊዋ ጠቁመዋል፡፡

በፀሐይ ጉልማ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version